የስሜት ህዋሳት እክል እና ትምህርታዊ ፕሮግራም ላይ አይነስዉራን ተማሪዎችን ሊሚያስተምሩ መምህራን ስልጠና ተሰጠ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በብርሃን የዓይነ-ስውራን አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ዛሬ(ሰኔ 9፣ 21047) ት/ቤቱ መምህራን የስሜት ህዋሳት እክል እና ትምህርታዊ ፕሮግራም የአይነስዉራን ተማሪዎችን እንዴት ማስተማርና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ እንዴት በንቃት መሳተፍ እችላሉ በሚል ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።
ስልጠናዉ የተሰጠዉ አይፒኦ (IPO) ድርጂት ጋር በመሆን ስሆን ስልጠናዉ አይነስዉራንን ለማስተማርና መረጃ መለዋወጥ ዙርያ ያጠነጠነና በቅርበት ከነሱ ጋር መስራት የሚያስችልነዉ ተገለጸ፡፡
የትምህርት ቤቱ ዋና ዳይረክር ወይዘሮ ዉብአለም ደበበ በረሐ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር በዚህ ስልጠና የማናቃቸዉን በአይነስዉራን ተመሪዎች ዙሪያ በአለም አቀፍ ባለሙያ ማግኘታችን ተማሪዎቹ አዉንም ብቃታቸዉንና ችሎታቸዉን እንዲያወጡና በሁሉም ዘርፍ ተሳትፎ እንዲኖራቸዉ የሚያደረግም ብለዋል፡፡





.